ተፈሪ መኰንን ረዥሙ የሥልጣን ጉዞ

ተፈሪ መኰንን ረዥሙ የሥልጣን ጉዞ በሚል ርዕስ እንደ አ.አ. በሐምሌ 1905 ዓ.ም. ለአንባቢዎች የቀረበው መጽሐፍ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ-ነገሥት ሆነው ኢትዮጵያን መምራት ከመጀመራቸው በፊት ደጃዝማች ተፈራ መኰንን ከሐረር ጠቅላይ ገዥነት ተነስተው በምን አኳኋን ባለሙሉ ሥልጣን አልጋወራሽ ለመሆን አንደበቁና ዘውድ እስከጫኑበት ጊዜ ድረስ የኢትዮጵያን መንግሥት ሲመሩ እንደቆዮ የሚያስረዳ ነው፡፡
ብዚዎች አንባቢዎች አንደሚያውቁት ከአፄ ምኒልክ ሕየወት ፍጻሜ በኋላ በአገራችን በያለበት እየተቀመመ የሚሠራጨው የአፈ ታሪክ ተፈሪ መኮንን የኢትዮጵያ መሪ ለመሆን የበቁት ልጅ ኢያሱን በኩዴታ ጥለው ንግሥት ዘውዲቱን በሐኪም መርፌ አስገድለው ነው የሚል ነው፡፡
ደራሲው በዚያን ዘመን የተካሄደውን የኢትዮጵያን ታሪክ ለረዥም ጊዜ ምርምርና ጥናት በማካሄድ
1ኛ. ልጅ ኢያሱ ከሥልጣን እንዴት እንደወረዱ ፣ ወይዘሮ ዘውዲቱ ምኒልክ ንግሥተ ነገሥታት ተብለው ዘውድ ለመጫን እንደበቁ
2ኛ. ለመንግሥቱ ሥራ አመራር የራስ መኰንን ልጅ ተፈሪ መኰንን ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴና አልጋ ወራሽ ሆነው እንደተመረጡ
3ኛ. ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለዩ ትክክለኛውን ታሪክ ለአንባቢዎች ለማቅረብ ደራሲው ብርቱ ጥረት አድርጓል፡፡

ውሳኔው የአንባቢውች ነው
ዘውዴ ረታ