የኤርትራ ጉዳይ

የኤርትራ ጉዳይ በዚህ ርዕስ ተጽፎ የቀረበው ታሪክ በሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የተመረኮዘ ነው፡፡
1ኛ. አብዛኛው የኤርትራ ሕዝብ ፣ ከባዕድ አገዛዝ ለመላቀቅና ወደ መሠረት አገሩ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ኢትዮጵያ ወይ ሞት ብሎ በመታገል ምን ያህል መከራና ፈተና እንደተቀበለ
2ኛ. የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ኤርትራን ከኢትዮጵያ ጋር ለማዋኃድ በአራቱ ኃያላን መንግሥታት ዳንነትና ቀጥሎ በተባበሩት መንግሥታት ሸንጎ ላይ ለብዙ ዓመታት ያደረገው ፋታ የሌለው ሙግት ምን ውጤት እንደሰጡ
3ኛ. በተባበሩ መንግሥታት ሸንጎ ላይ ኤርትራ በፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ጋር እንድትቀላቀል ፣ ፍርዱ እንዴት እንደተወሰነና፣ ከዚያም ለአሥር ዓመታት የተካሄደው የፌዴሬሽን አስተዳደር በምን መልክ ይሠራበት እንደነበረና በኃላም በምን አኳኋን እንደፈረሰ

እውነተኛውን ታሪክ የኢትዮጵያና የኤርትራ ሕዝቦች እንዲያውቁት በዝርዝር የተዘጋጀና ከፍ ያለ ጥረት የተደረገበት ነው፡፡
መልካም ንባብ
ዘውዴ ረታ