የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት

ርዕሱ እንደሚያስረዳው ኢትዮጵያን ለአርባ አምስት ዓመታት ያህል በንጉሠ ነገሥትነት ሲያስተዳድሯት የኖሩት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የመጀመሪያዎቹን የሃያ አምስት ዓመታት የመንግሥታቸውን አመራር ታሪክ ይህ መጽሐፍ ተንንትኖ አቅርቧል፡፡
በዚህ በሃያ አምስት ዓመታት ዘመነ መንግሥት ውስጥ
1ኛ . የፋሽስት ጣሊያን ወረራ አመጣጥ
2ኛ. የኢትዮጵያን ነጻነት ለማዳን ንጉሠ ነገሥቱ በዤኔቭ የመንግሥታት ማህበር ሸንጎ ላይ ያደረጉት ሙግትና በመጨረሻም ሊግ ኦፍ ኔሽን ያደረገው አሳዛኝ ውሳኔ
3ኛ. ሙሶሊኒ ከሂትለር ጋር ተሰልፎ የአውሮፓን መንግሥት በጦር ሲወጋ ፣ እንግሊዞች የኢትዮጵያን ነፃነት ለማስመለስ አገራችንን ከያዙ በኋላ የጫኑብን የሞግዚት አስተዳደር እንዴት እንደነበረ
4ኛ. ነፃነታችን ከፋሽስት እጅ ከተመለሰ በኋላ ከእንግሊዞች የሞግዚት አስተዳደር ለመላቀቅ ምን ያህል ድካም እደጠየቀ
5ኛ. ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በምሥጡር ወደ ስዌዝ ካናል ተጉዘው ከአሜሪካው መሪ ከፕሬዚዳንት ሩዝቬልት ጋር ያደረጉት ንግግር
6ኛ. የኢትዮጵያ ከእንግሊዞች የሞግዚት አስተዳደር ከተላቀቀች በኋላ በአገር ውስጥ የሁለት ሰዎች (መኮንን ሀብተወልድና ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ) የሥልጣን አነሳስና ትብብር ንጉሠ ነገሥቱን ምን ያህል እንደአሳሰባቸው
7ኛ. ከእነዚህ ከሁለቱ ሰዎች መካከል የሥልጣን ኃይላቸው አስጊ ሆኖ የተገመተውን ፣ ጸሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስን በሽረት ከካቢኒያቸው ለማራቅ ንጉሠ ነገሥቱ የወሰዱት እርምጃ
በዚህ መጽሐፍ ውስጥ በዝርዝር ስለተገለጸ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይህንን እውነተኛ ታሪክ አንብቦ ለመረዳት ይችላል፡፡
ዘውዴ ረታ